ተሐድሶ - እንደ ማህበረ ቅዱሳን
(ሰንበቴ፣ ነሐሴ 23፡ 2003 ዓ.ም.)
በአሁኑ ወቅት ማህበረ ቅዱሳን በቤተክርስቲያን ጀርባ ላይ በመስፈንጠር አገርን የመምራት ህልሙን ለማሳካት በጭፍን በያዘው አቅጣጫው “ተሐድሶ” የሚል ነጠላ ዜማ እንደለቀቀ ተረጋገጠ፡፡
ይህ የተረጋገጠው በማሕበሩ ሚዲያ፣ በስውርና ግልጽ አመራሮቹ፣ ከቅዱሳን በረከት ለማግኘት ሳይሆን መንግሥትን በደቦ ለማማት ያመቻቸው ዘንድ በተቋቋሙ ጽዋ ማህበራትና በጭፍን በሚራመዱ አባላቱ የኢትዮጵያን ሕዝብ ለማተራመስ በማካሄድ ላይ በሚገኙት እንቅስቃሴ ነው፡፡
በማኅበረ ቅዱሳን አገላለጽ “ተሐድሶ” ማለት በተግባር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ተሰግስገው ሃይማኖትና ሥርዓትን ለመለወጥ የሚንቀሳቀሱ አካላት ሳይሆን፡-
1.በመንፈሳዊ አገልግሎታቸውና በጸጋ እግዚአብሔር ጎልተው ለወጡ ነገር ግን የማህበሩ አባላት ወይም ደጋፊ ላልሆኑ አካላት
2.በካሴትና በመጻሕፍቶች ሽያጭ ማህበሩንና ደጋፊዎቹን ከገበያ በማስወጣት ለከፍተኛ ኪሳራ ለዳረጉ ሃይሎች
3.ማህበሩ በስውርም ሆነ በግልጽ የሚያራምደውን ሀገርንና ቤተ ክርስቲያንን የሚያወድም አካሄድ እንዲያርም በግልጽ ለሚነግሩትንና ባለማስተካከሉም አቋም ለያዙ
4.የጎ2 ወይም የሸ ስውር አመራርና የዘር አሰራው ደጋፊና ተንበርካኪ ላልሆኑ
5.ማህበሩን ለማጋለጥ የሚያስችላቸው መረጃ ላላቸው
6.በማህበሩ ላልተጠመቁና ለቤተ ክርስቲያን መዋቅራዊ አሰራር መጠናከር ለሚቀኑ
7.እውነቱን እውነት ሐሰቱን ሐሰት ለሚሉ
8.በነገይቱ ቤተ ክርስቲያን አማራጭ የለውጥና የጠራ አገልግሎት ኃይል በመሆን ሊቀድሙት ለሚችሉ
9.… እንቀጥላለን የቤተ ክርስቲያን ልጆች የሚሰጥ ስም ነው፡፡
ማህበረ ቅዱሳን ይህ አቅጣጫው በአንዳንድ አካላት፣ ሰንበት ትምህርት ቤቶችና ካህናት ቢነቃበትም “አይመልሰኝ” ብሎ እየሸመጠጠ ይገኛል፡፡
ማህበሩ አሁን በያዘው አቅጣጫ “ተሐድሶ ሰዎችን ላጋልጥ ነው” በማለት በስልክ የጽሑፍ መልእክትና በኢሜል ሕዝብ ይሰበስባል፣ የተሰበሰበውንም ሕዝብ ስሜት ግለት ውስጥ ከጨመረ በኋላ ዲ. ዳንኤል እንደጻፈው “ድርጅቶችን ለማለት ፈልገን ነው” በማለት ያስቀይሳል፣ በአጋጣሚ የሚጣሉት ሲያገኝም ተመሳሳይ ድስት ውስጥ ጨምሮ ይቀቅላቸዋል፣ ወዘተ እንጂ በርግጥም ተሐድሶዎቹን በማስረጃ ደግፎ አያስረዳም የማስረዳት አቅምም የለውም፡፡ ይህ አካሄድ ማህበሩ እንደ ሃያላን አገሮች ”ሽብርተኞች“ በሚል ፈሊጥ ስም እየለጠፈ የማተራመስና የፖለቲካ ልምድ ለመቅሰም አስቦ የሚያደርገው እንደሆነ ብዙዎች ይስማሙበታል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ አሁን ያበደ ውሻ ሆኖ ሁሉን በመልከፍ ላይ የሚገኘው ማህበር ከአቡነ ጳውሎስና ከነበጋሻው ጋር እንዲያስታርቋቸው እጅጋየሁን አላስገባ አላስወጣ እያሉ እንደሆነ ለመረዳት ተችሏል፡፡
Monday, August 29, 2011
Friday, August 26, 2011
የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን ነሐሴ 15 ቀን 2003 ዓ.ም. አነጋገሩ፡፡
የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ ጳውሎስን ነሐሴ 15 ቀን 2003 ዓ.ም. አነጋገሩ፡፡
(ሰንበቴ፡ ነሐሴ 20 2003 ዓ.ም.)የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች በአንድ በኩል በውስጥም ሆነ በውጭ እየደረሰባቸው ከሚገኘው ከፍተኛ ኪሳራና መበጥበጥ ለማገገም በሌላ በኩል እንደ ተለመደው ለጊዜው የማድፈጥ ሂደታቸውን መቀጠላቸውን የድብቅ ልሳናቸው የሆነው ደጀሰላም በመጠቆም ላይ ይገኛል፡፡
ማኅበርተኞቹ ከተጋረጠባቸው ችግር ለማምለጥ በስውርና በቆዩ አባሎቻቸው እንዲሁም በቤተክርስቲያኒቱ ላይ ተጣብቀው በገዳማት ስም ማኅበሩ ከሚሰበስበው ገንዘብ በገፍ እየፈሰሰላቸው ቤተ ክርስቲያንን ለመሸጥ በተስማሙ ቢጸ ሐሳውያን ተጠቅመው ከሞት አፋፍ ለመትረፍ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡
ለዚህም ማሳያ የሚሆነን እሁድ ነሐሴ 15 ቀን 2003ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ከብጹዕ ወቅዱስ አብነ ጳውሎስ ጋር ያደረጉት ውይይት ነው፡፡ ማኅበሩ በዚህ ቀጠሮ ከፓትርያርኩ ጋር ለመገናኘት እንዲችል እንደ ድልድይ ያገለገሉት፡- የፓትርያርኩ ጠባቂ ሙሉጌታ በቀለና አገልጋይ አባ እንቆ ሲሆኑ እነርሱም የሙሰኝነት ልምዱ ባላቸው በቅርብ ጊዜ የቤተክህነቱ ሕዝብ ግኑኝነት ከተባሉት (የቤተ ክህነቱ ዋነኛ ጉቦ አቀባባይና ተቀባይ ዳዊት) በኩል በርካታ ሺ ገንዘብ ለማውጣት ፈቅዷል፡፡ ለቀጠሮው መሳካት በዘማሪነት የሚታወቁ አንዲት ሴት ያበረከቱት አስተዋጽኦም የማይናቅ ነው፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩም ሕግንና ሥርዓትንና ቀኖናን ባልተከተለ መልኩ ማኅበሩ በየሆቴሉ፣ አዳራሾችና መንደር ለመንደር እያካሄደ የሚገኘው ‹‹የተሐድሶ እወጃ›› የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና ያልተከተለ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው፣ ማኅበሩ ኦዲት እንዲደረግ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በድጋሚ የተላለፈለትን መመሪይ በአስቸኳይ እንዲያስፈጽሙ፣ ለቤተክርስቲያን የሚሰጡትን አገልግሎትም ሕግንና ሥርዓትን ተከትለው እንዲፈጽሙ፣ በግልጽ የተገኙበት ችግር ሲታወቅባቸው ከማስቀየስ እንዲቆጠቡ፣ ሰከን ብለው ራሳቸውን እንዲመለከቱ የሁሉንም የቤተ ክርስቲያን ልጆች አገልግሎት እንዲያከብሩ አሳስበዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሕገ ወጥ አካሄዳቸውን ሳያውቁ የሚከተሉትን ለማጀገን ታስቦ የማኅበሩ ‹‹ዘመድ›› በሆኑ ብሎጎች የተዘገበው ዘገባ ሐሰት መሆኑንና ይህ አካሄድ ማኅበሩ ላለፉት 20 ዓመታት ሲፈጽመው የቆየ ቢሆንም አሁን ግን ሁሉም ነገር ቁልጭ ብሎ ለሁሉም መታየት መቻሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በመጨረሸም ፓትርያርኩ “ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ ለምትሠሩት ሥራ የአባት በር የሚዘጋ አለመሆኑንና ይህ በሆነበት ሁኔታ የሚረዱንን ልጆቻችንን ሁሉ ያለ አድልዎ በማስተናገድ የየድርሻቸውን እንዲወጡ ከማድረግ አንቆጠብም፡፡ ለእኛ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን ናቸው፡፡ ባልተጨበጠ ነገር መለጣጠፍም ጉዳት እንጂ ጥቅም አይኖረውም፡፡ ያለ ነገር ካለ ሁሉንም አቅርቡ፤ ከሌለ መኖር ያለብን እኛ ብቻ ነን አትበሉ፡፡ በየጊዜው የሚሰማባችሁ አቤቱታ ይህ ነው፡፡ በመዋቅር ላስቀመጥናቸው ታዘዙ፡፡ ከሰንበት ት/ቤት መምሪያው ጋር ያላችሁን አልታዘዝ ባይነት ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱም ደግማችሁ ገልጻችኋል፡፡ እኛ ካላዘዝናችሁ የሚያዛችሁ ማነው? …” በማለት መልዕክት አስተላልፈውላቸዋል፡፡
እንደለመዱት አጭበርብረው ማለፍ የተሳናቸው የማኅበሩ አባላትም በቅርቡ (ማኅበሩንና አጋሮቹን) አስመልክቶ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተላለፈውን መመሪያና ደብዳቤ እንደሚቀበሉና መመሪያውም ትክክል እንደሆነና እንደሚደግፉት በጨው በታጠበ ዓይናቸው አረጋግጠው ተሸኝተዋል፡፡
(ሰንበቴ፡ ነሐሴ 20 2003 ዓ.ም.)የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች በአንድ በኩል በውስጥም ሆነ በውጭ እየደረሰባቸው ከሚገኘው ከፍተኛ ኪሳራና መበጥበጥ ለማገገም በሌላ በኩል እንደ ተለመደው ለጊዜው የማድፈጥ ሂደታቸውን መቀጠላቸውን የድብቅ ልሳናቸው የሆነው ደጀሰላም በመጠቆም ላይ ይገኛል፡፡
ማኅበርተኞቹ ከተጋረጠባቸው ችግር ለማምለጥ በስውርና በቆዩ አባሎቻቸው እንዲሁም በቤተክርስቲያኒቱ ላይ ተጣብቀው በገዳማት ስም ማኅበሩ ከሚሰበስበው ገንዘብ በገፍ እየፈሰሰላቸው ቤተ ክርስቲያንን ለመሸጥ በተስማሙ ቢጸ ሐሳውያን ተጠቅመው ከሞት አፋፍ ለመትረፍ ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ ይገኛሉ፡፡
ለዚህም ማሳያ የሚሆነን እሁድ ነሐሴ 15 ቀን 2003ዓ.ም ከሰዓት በኋላ የማኅበረ ቅዱሳን አመራሮች ከብጹዕ ወቅዱስ አብነ ጳውሎስ ጋር ያደረጉት ውይይት ነው፡፡ ማኅበሩ በዚህ ቀጠሮ ከፓትርያርኩ ጋር ለመገናኘት እንዲችል እንደ ድልድይ ያገለገሉት፡- የፓትርያርኩ ጠባቂ ሙሉጌታ በቀለና አገልጋይ አባ እንቆ ሲሆኑ እነርሱም የሙሰኝነት ልምዱ ባላቸው በቅርብ ጊዜ የቤተክህነቱ ሕዝብ ግኑኝነት ከተባሉት (የቤተ ክህነቱ ዋነኛ ጉቦ አቀባባይና ተቀባይ ዳዊት) በኩል በርካታ ሺ ገንዘብ ለማውጣት ፈቅዷል፡፡ ለቀጠሮው መሳካት በዘማሪነት የሚታወቁ አንዲት ሴት ያበረከቱት አስተዋጽኦም የማይናቅ ነው፡፡
ቅዱስ ፓትርያርኩም ሕግንና ሥርዓትንና ቀኖናን ባልተከተለ መልኩ ማኅበሩ በየሆቴሉ፣ አዳራሾችና መንደር ለመንደር እያካሄደ የሚገኘው ‹‹የተሐድሶ እወጃ›› የቤተ ክርስቲያንን ቀኖና ያልተከተለ በመሆኑ ጥብቅ ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው፣ ማኅበሩ ኦዲት እንዲደረግ በጠቅላይ ቤተ ክህነቱ በድጋሚ የተላለፈለትን መመሪይ በአስቸኳይ እንዲያስፈጽሙ፣ ለቤተክርስቲያን የሚሰጡትን አገልግሎትም ሕግንና ሥርዓትን ተከትለው እንዲፈጽሙ፣ በግልጽ የተገኙበት ችግር ሲታወቅባቸው ከማስቀየስ እንዲቆጠቡ፣ ሰከን ብለው ራሳቸውን እንዲመለከቱ የሁሉንም የቤተ ክርስቲያን ልጆች አገልግሎት እንዲያከብሩ አሳስበዋል፡፡
ይህ በእንዲህ እንዳለ ሕገ ወጥ አካሄዳቸውን ሳያውቁ የሚከተሉትን ለማጀገን ታስቦ የማኅበሩ ‹‹ዘመድ›› በሆኑ ብሎጎች የተዘገበው ዘገባ ሐሰት መሆኑንና ይህ አካሄድ ማኅበሩ ላለፉት 20 ዓመታት ሲፈጽመው የቆየ ቢሆንም አሁን ግን ሁሉም ነገር ቁልጭ ብሎ ለሁሉም መታየት መቻሉን ለማወቅ ተችሏል፡፡
በመጨረሸም ፓትርያርኩ “ሕግና ሥርዓትን ተከትሎ ለምትሠሩት ሥራ የአባት በር የሚዘጋ አለመሆኑንና ይህ በሆነበት ሁኔታ የሚረዱንን ልጆቻችንን ሁሉ ያለ አድልዎ በማስተናገድ የየድርሻቸውን እንዲወጡ ከማድረግ አንቆጠብም፡፡ ለእኛ ሁሉም ኦርቶዶክሳውያን ልጆቻችን ናቸው፡፡ ባልተጨበጠ ነገር መለጣጠፍም ጉዳት እንጂ ጥቅም አይኖረውም፡፡ ያለ ነገር ካለ ሁሉንም አቅርቡ፤ ከሌለ መኖር ያለብን እኛ ብቻ ነን አትበሉ፡፡ በየጊዜው የሚሰማባችሁ አቤቱታ ይህ ነው፡፡ በመዋቅር ላስቀመጥናቸው ታዘዙ፡፡ ከሰንበት ት/ቤት መምሪያው ጋር ያላችሁን አልታዘዝ ባይነት ለጠቅላይ ቤተ ክህነቱም ደግማችሁ ገልጻችኋል፡፡ እኛ ካላዘዝናችሁ የሚያዛችሁ ማነው? …” በማለት መልዕክት አስተላልፈውላቸዋል፡፡
እንደለመዱት አጭበርብረው ማለፍ የተሳናቸው የማኅበሩ አባላትም በቅርቡ (ማኅበሩንና አጋሮቹን) አስመልክቶ በቅዱስ ፓትርያርኩ የተላለፈውን መመሪያና ደብዳቤ እንደሚቀበሉና መመሪያውም ትክክል እንደሆነና እንደሚደግፉት በጨው በታጠበ ዓይናቸው አረጋግጠው ተሸኝተዋል፡፡
Subscribe to:
Posts (Atom)