Thursday, September 15, 2011

ማኅበረ ቅዱሳን በውጪ የሚገኙ አባላቱ 1000 ዶላር በነፍስ ወከፍ እንዲያሰባስቡ ግዴታ ጣለባቸው

(ሰንበቴ፤ መስከረም 3 2003 ዓ.ም.) ማኅበረ ቅዱሳን በውጪ የሚገኙ አባላቱ 1000 ዶላር በነፍስ ወከፍ እንዲያሰባስቡ ግዴታ ጣለባቸው::


(ሰንበቴ፤ መስከረም 3 2003 ዓ.ም.)
ማህበረ ቅዱሳን ከኢትዮጵያ ውጪ የሚኖሩ አባላቱ እያንዳንዳቸው 1000 ዶላር በማሰባሰብ ቤተ ክርስቲያንንና አገርን የማወክ ተግባሩን እንዲያግዙለት ጠየቀ፡፡

ማኅበሩ የመስቀል በዓልንና የጥቅምቱን ሲኖዶስ ለመበጥበጥ የያዘውን ዕቅድ በታለመለት መልኩ እያከናወነ እንደሚገኝ የውስጥ ምንጮቹ የጠቆሙ ሲሆን የተለያዩ ተመሳሳይ ተግባራቱን ለማከናወን የሚያስችለውን እገዛም አባላቱ በአስቸኳይ እንዲያሟሉለት አሳስቧል፡፡

ማህበሩ ከገጠመው የገንዘብ እጥረት ለማገገም የተለያዩ ስልቶችን ነድፎ በመንቀሳቀስ ላይ ሲሆን በገዳማትና በተለያዩ መንፈሳዊ ምክንያቶች የሚሰበስበውንም ብር ጳጳሳቱን በየመኖሪያ ክፍላቸው እየተከታተለ በገንዘብና በቁሳቁስ ለማንበርከክና ሌሎች ጥቅመኞቹንም (ወልደ ሩፋኤል ፈታሂ፣ ደስታ፣ ዘሪሁን ሙላቱ፣ ዘመድኩን በቀለ፣ …) በጠራራ ጸሐይ ውስኪ ለመጠጣት እንዲያስችላቸው በገፍ እያፈሰሰላቸው የሚገኝ መሆኑን በርካታ አባላቱ አረጋግጠዋል፡፡ የዚህ ገንዘብም ዋና ምንጮችም በአሜሪካ የሚገኙ የዋህ ምዕመናንና በመርካቶ ውስጥ ‹‹ቤተክርስቲያንን እንታደግ›› በሚል የተሰባሰበው ቡድን መሆናቸው ታውቋል፡፡

በማህበሩ ከአምስት የሚበልጡት የተከፋፈሉ ቡድኖች የየራሳቸው አጀንዳ ይዘው በመንቀሳቀስ እርስ በርሳቸው በመበላላት ላይ የሚገኙ ሲሆን ማህበሩን መተዳደሪያ ያደረጉ አንዳንድ ሰራተኞችም ቤተክርስቲያኒቱ እንጀራ (ስራ) እንዲትሰጣቸው ጥያቄ አቅርበዋል፡፡ በማያያዝም ማህበሩ በተቃዋሚዎቹ ላይ ሰብአዊ ጥቃት ለማድረስ የሚያስችሉትን እንቅስቃሴዎች የማጅራት መቺዎችን፣ ነፍሰ ገዳዮችንና በጥላ ወጊነት የጥንቆላ ስራ ችሎታ ያላቸውን አካላት በማሰማራት አፈጻጸሙን እየተከታተለ የሚገኝ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ ማህበረ ቅዱሳን የውስጥ ችግሮቹን በማስቀየስ ለማለፍ እንዲያስችለው የነደፈው ‹‹ተሐድሶ›› የሚለው ስልት በብዙዎች ዘንድ እየተነቃበት ስለመጣ መሪዎቹ እንዳበደ ውሻ በየቦታው ለመልከስከስ እንደተገደዱ ለማየት ተችሏል፡፡ ማንነቱም እንዳይታወቅ ሽፋን የሚሰጡት የ‹‹መንግስት ደህንነት›› ሰራተኞች ነን ባዮች ጥንቃቄ የማያደርጉ ከሆነ ራሱ መንግስትንም ወደ ከፍተኛ ቀውስ ሊከቱት እንደሚችሉ አንዳንዶች አንዳንድ ምንጮች በመጠቆም ላይ ይገኛሉ፡፡

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያንን በመሸጥ ወደ ካቶሊክነት ገብተው በይቅርታ የተመለሱትና ፖለቲከኞችን በማስተባበር ሞያ የተካኑት አቡን ገብርኤል ሰሞኑን አዲስ አበባ ሲገቡ የማህበሩ አባላት ባደረጉላቸው ታላቅ ድግስ ውስኪና ሻምፓኝ ሲራጩ ማምሸታቸው ታውቋል፡፡ አባላቱ በጥቅምቱ ሲኖዶስ ለሚበጠብጡላቸው ጳጳሳት ምግብና መጠጡን በየክፍላቸው ሲያመላልሱ ያመሹ መሆኑን የውስጥ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

2 comments:

  1. Hi Bloggers,
    This seems a source of good information apart from needs for corrections on some letters.
    God Bless You

    ReplyDelete
  2. እውነትም... ማህበረ ቅዱሳን የውስጥ ችግሮቹን በማስቀየስ ለማለፍ እንዲያስችለው የነደፈው ‹‹ተሐድሶ›› የሚለው ስልት በብዙዎች ዘንድ እየተነቃበት ስለመጣ መሪዎቹ እንዳበደ ውሻ በየቦታው ለመልከስከስ እንደተገደዱ ለማየት ተችሏል...

    ReplyDelete