Monday, September 5, 2011

ማህበረ ቅዱሳን የመስቀል በዓልን በማስታከክ ሽብር ለመፍጠር በዝግጅት ላይ ነው፡፡

(ሰንበቴ፡ ነሐሴ 30፡ 2003 ዓ.ም.) በሰንበት ት/ቤቶች ማስተባበሪያ ስር እተዳደራለሁ የሚለው ማህበረ ቅዱሳን በአዲስ አበባ የሞከበረውን የ2004 ዓ ም የመስቀል በዓል ለመበጥበጥ የሚያስችለው እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ ነው፡፡ ማህበሩ በበዓሉ ላይ የሰንበት ት/ቤቶችን ወክለው መዘሙርና ትርኢት የሚያቀርቡ የአዲስ አበባ ወጣቶችን በተለያዩ አደረጃጀቶችን ተጠቅሞ በመቀስቀስ ላይ የሚገኝ ሲሆን በበአሉ ላይ ጥቁር ልብ አስለብሶ ሙሾ ለማስወረድ ዝግጅቱን አጠናቆ ወደስራ ገብቷል፡፡

ይህ ድርጊት የአገሪቱንና የቤተ ክርስቲያኒቱን መልካም ገጽታ በማጨለም ራሱን ለማጉላት ብሎም የህዝብን ትኩረት ለማስቀየስ የፈጠረው መሆኑ ተደርሶበታል፡፡

ይህ በእንዲህ እንዳለ መሰሪው ማህበር ንቡረ እድ ኤልያስን በመዝለፍ በደጀሰላም ላይ የዘገበውን ዘገባ ከብሎጉ ላይ ማጥፋቱም ተረጋግጧል፡፡ ድርጊቱም የንቡረ እዱን ቁጣ ያባባሰ እና ይህ መደረጉ በተራ ወሬዎች ወይም በተለያዩ ቁሳዊ ጥቅሞች እንደሚደልሏቸው ሰዎች የአቅዋም ለውጥ ለማሳየት የማያስገድዳቸው መሆኑን አስረግጠው መግለጣቸውን ተከትሎ የተፈጸመ መሆኑ ተረጋግጧል፡፡

ማህበሩ የአቡነ ጳውሎስን ሞት በማፋጠን የሚፈልጋቸውን ፑፔት ጳጳሳት በማስቀመጥ እንደልቡ ለመጋለብ የቋመጠ ሲሆን ይህን ከማድረግ ሊያደናቅፉት የሚችሉትን ሁሉ በተሐድሶነት በመፈረጅ ስልቱ ቀጥሎበታል፡፡ እስካሁን ድረስም ይህ ተሐድሶ የሚለው ጽዋ ለፓትርያርኩ፣ ለአቡነ ፋኑኤል፣ ለአቡነ መልከ ጼዴቅ (ማህበሩ የመጨረሻውን ማርሽ ቀይሮ የሞታቸውን ዜና አሳምሮ በመዘገብ ወዳጃቸው ለመምሰል ቢሞክርም በርሳቸው ላይ የሠራውን ያውቀዋል)፣ አቡነ እስጢፋኖስ፣ አቡነ ሳዊሮስ፣ አቡነ ጎርጎርዮስ፣ አቡነ ያሬድ፣ አቡነ ሚካኤል (ማህበሩ የመጨረሻውን ማርሽ ቀይሮ የሞታቸውን ዜና አሳምሮ በመዘገብ ወዳጃቸው ለመምሰል ቢሞክርም በርሳቸው ላይ የሠራውን ያውቀዋል)፣ መጋቤ ብሉይ ሠይፈ ሥላሴ (ማህበሩ የመጨረሻውን ማርሽ ቀይሮ የሞታቸውን ዜና አሳምሮ በመዘገብ ወዳጃቸው ለመምሰል ቢሞክርም በርሳቸው ላይ የሠራውን ያውቀዋል)፣ ንቡረ እድ ኤልያስ፣ አባ ሰረቀ፣ … ደርሷቸዋል፡፡ ሌሎቹም የጠነከረ አቋም ይዘው ሲገኙ ወደፊት የሚቀበሉት ጽዋ ይሆናል፡፡ ምን ያለበት ምን አይችልም እንዲሉ አንዳንዶቹም ከዚህ ስም ልጠፋ ለማምለጥና ጉዳቸው እንዳይገለጥ በማህበሩ ላይ የተጣበቁ ለማስመሰል እየተጣጣሩ እንደሚገኙ ለመረዳት ተችሏል፡፡

5 comments:

  1. Let us pray for them to be on track.

    ReplyDelete
  2. senbtewoch,
    Ewnetegna ye zena amarach yeseten egzixbehr yimesgen!

    ReplyDelete
  3. Dear Senbete,

    It is really surprising to see these all bishops to always blame Abune Paulos while they are killing their dioceses due to corruption, unfaithfulness to God and the believers.

    Most of the Bishops now do have more than one building of houses in Addis Ababa and in other cities. They are counting millions of Birr from their account and truth are revealing at the end of their life. Such Bishops and Arch Bishops are trying to act as if they are standing for our church to guard the Dogmas, Traditions and Canons of our church though they are not even a mere believer.

    Mahibere kidusan doesn't tell us about the problems of such Bishops as they are roaring what the mahiber has breathed on them.

    Who is Abune Timotewos, Abune Samuel, Abune Lukas, ... do mahibere kidusan and the Arch Bishops think that they are able to hide the truth the public knows?

    I really comment on all of them to change their mind set and start to confess and lead the gangsters both from mahibere kidusan and begashaw to the right way otherwise they will do it unwillingly forced by the arm of God.

    Thanks and God Bless you for your dedication

    ReplyDelete
  4. Senbetewoch,

    Here in DC Daniel, Ephrem with the leadership of Mahibere Kidusan and Abune Abraham are working hardly to split the church from the Synod in Addis.

    Abune Abraham has recently paid 50,000USD from his pocket to someone who knows his personal story and was on the way to publish it. Do you think that Abune Abraham can have that much money saved from his monthly salary?????????????
    Share on THEM!!!!!!


    You people, please confess for your sins!

    ReplyDelete